ነሐሴ 2024

Selam, ለሰላም, ዜና

በሀረሪ ፖሊስ ኮሚሽን የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊሳዊ አገልግሎት አባላት በሀረር ከተማ አራተኛ የገብርኤል በአል የሚከበርበትን ስፍራን አፅድተዋል።

በሀረሪ ፖሊስ ኮሚሽን የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊሳዊ አገልግሎት አባላት በሀረር ከተማ አራተኛ የገብርኤል በአል የሚከበርበትን ስፍራን አፅድተዋል። በሀረሪ ፖሊስ ኮሚሽን የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊሳዊ አገልግሎት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ግሩም ውብሸት የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ከማህበረሰብ አቀፍ ፖሊሳዊ አገልግሎት አባላት ጋር በመተባበር በሀረር ከተማ አራተኛ የሚገኘው የቁልቢ ገብርኤል አመታዊ የንግስ በአል የሚከበርበትን ስፍራ ማፅዳታቸውን ገልፀዋል። በተመሳሳይም የሰላም አደረጃጀቶቹ በሀረር […]

ለሰላም, ዜና, የሰላም እና ደህንነት

የገብርኤል አመታዊ የንግስ በአል በሰላም መጠናቀቁ ተገለፀ

የሀረሪ ክልል ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሀላፊ አቶ ቶፊቅ መሀመድ እንደገለፁት በቁልቢ ገብርኤል ከተከበረው አመታዊ የንግስ በአል በተጨማሪ በሀረር ከተማ አራተኛ ገብርኤል የተከበረው በአልም ፍፁም ሰላም በሰፈነበት መልኩ ተከብሮ በሰላም መጠናቀቁን ጠቁመዋል። በአሉ በሰላም መጠናቀቁ ሀረር የሰላም፣ የፍቅርና የመቻቻል ከተማ መሆኗና ህዝቦቿም ሰላም ወዳድ መሆናቸውን አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል። በአሉ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ አስተዋፅኦ ላደረጉት

ለሰላም, የሰላም እና ደህንነት

“ለሀገሩ ዋጋ የከፈለ ሠው ማንም ቢሆን የተከበረ ነው “

“ለሀገሩ ዋጋ የከፈለ ሠው ማንም ቢሆን የተከበረ ነው “ የኢትዮጵያ ታሪክ ዋነኛ መሠረቱ ወታደር ነው አይተኬ ህይወቱን ገብሮ ሀገርና ትውልድ ያጸናል፤ ከሠፈርና ከመንደር የተሻገረ የላቀ አላማ እና መስዋዕትነት የያዘ ሠራዊት ሀገርን ይታደጋል። የሀገር መከላከያ ሠራዊት በየደረጃው የገጠመው ፈተና የተሻለ ደረጃና አቅም ያለው ሆኖ ዳግም እንዲፈጠር አስችሎታል፤ ይህን አቅሙን በመጠቀም በበለጠ ፍቅርና ታማኝነት ሊያገለግል ይገባል። የሀገር

ለሰላም, ዜና

በሀረሪ ክልል የተጀመረው አገራዊ ምክክር ቀጥሎ እየተካሄደ ይገኛል።

የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀረሪ ክልል የጀመረው አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት አሁንም ቀጥሎ እየተካሄደ ይገኛል። ኮሚሽኑ ባለፉት 3 ቀናት የወረዳ ተወካዮችን በማወያየት አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደቱን ያጠናቀቀ ሲሆን በዛሬው ዕለት ሁተኛ ዙር አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደቱን አስጀምሯል። እየተካሄደ በሚገኘው አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት የህብረተሰብ ተወካዮች፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የመንግስት አካላት እንዲሁም የማህበራትና ተቋማት ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛል።

ለሰላም, መግለጫዎች, ዜና

የአመለካከትና የተግባር አንድነትን በማጎልበት የክልሉን የብልፅግና ጉዞ ለማስቀጠል ርብርብ ይደረጋል- አቶ ጌቱ ወዬሳ

የአመለካከትና የተግባር አንድነትን በማጎልበት የክልሉን የብልፅግና ጉዞ ለማስቀጠል ርብርብ ይደረጋል- አቶ ጌቱ ወዬሳ የአመለካከትና የተግባር አንድነትን በማጎልበት የክልሉን የብልፅግና ጉዞ ለማስቀጠል ርብርብ እንደሚደረግ የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ ገለፁ። የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ በተጠናቀቀው የ2016 በጀት ዓመት ለውጥ አምጭ እሳቤዎችን በመላበስና በመተግበር ፣ የህዝቡን የአብሮነት እና

ለሰላም

የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ የውስጠ ፓርቲ የአመራር ግምገማ ማካሄድ ጀመረ

የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ አመታዊ የአመራር የውስጠ ፓርቲ ግምገማ ማካሄድ ጀምሯል በግምገማ መርሃ ግብሩ መድረክ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ ብልፅግና ፓርቲ የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ ትልቅ ራዕይ ሰንቆ እየሰራ ይገኛል ። በተለይም አመራሩ በስናምግበሩ የታነፀ በእውቀት፣ በክህሎትና በአፈፃፀም ብቃቱ የላቃ አመራር ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ ስራዎች ሲሰሩ መቆየቱን

መግለጫዎች

በሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት የሚከናወኑ የመሰረተ ልማት ስራዎች ከመንገድ ያላቸው ርቀት መጠን (setback) በሚመለከት ደንብ አውጥቶ ወደ ተግባር መገባቱ ይታወሳል።

በወጣው ደንብ መሰረትም የሚከናወኑ ግንባታዎች በ30 ሜትርና ከዚያ በላይ ስፋት ካላቸው የዋና ዋና አውራ መንገዶች ቢያንስ 5 ሜትር ርቀው መከናወን አለባቸው። ከ20 እስከ 30 ሜትር ስፋት ካላቸው የሁለተኛ ደረጃ መንገዶች ቢያንስ 4 ሜትር ርቀት እንዲሁም ከ15 እስከ 20 ሜትር ስፋት ካለው የሰብሳቢ መንገድ ቢያንስ 3 ሜትር ርቀት መጠበቅ እንዳለባቸው ያስቀምጣል። ከዚህ በተጨማሪም ከ6 እስከ 15

Selam, ለሰላም, መግለጫዎች

በክልሉ በያዝነው የበጀት አመት የህዝቡን ፍላጎት መሠረት ያደረጉ የልማት ስራዎች በትኩረት ይሰራል:- አቶ ኦርዲን በድሪ

የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በክልሉ በ2017 በጀት ዓመት ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎችን በሚመለከት እንዳሉት የገቢ መሰረት በማስፋት ገቢን አሟጦ ለመሰብሰብ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ገልፀዋል። በክልሉ የቱሪዝም ልማት ስራዎች እንዲጠናከሩ ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣል ብለዋል። በጤና አገልግሎት፣ በትምህርት ጥራት ፣ እንዲሁም በግብርና ዘርፎ ምርትና ምርታማነትን የማሳደግ ስራ በልዩ ትኩረት ይከናወናል ብለዋል። በከተማው የተጀመረው የኮሪደር

Scroll to Top