ለሰላም

Selam, ለሰላም, በጎ ፈቃድ, ዜና

በሐረሪ ክልል የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ “የመስቀል ደመራ በዓል በማስመልከት የፅዳት መርሃ ግብር ተከናወነ

የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሰራተኞች ፣የፖሊስ ኮሚሽን አባላት ፣የወረዳ ሰላም አደረጃጀቶች፣ የሀይማኖት አባቶች በጋራ በመሆን የሀረርን የአብሮነት እሴት በሚገልፅ መልኩ የዘንድሮው የመስቀል ደመራ በዓል በሚከበርበት ቦታ የፅዳት ዘመቻ አካሂደዋል። በዚህ የጽዳት ዘመቻ ላይ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አባቶች ከሙስሊም እምነት አባቶችና ወንድሞች ፣ከፕሮቴስታንት እምነት አባቶች በጋራ የመስቀል ደመራ በአል ሀይማኖታዊ ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር መልካም ምኞታቸውን በመግለፅ […]

Selam, ለሰላም, ዜና

የሀረሪ ክልል ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ የሚከበረው የደመራ እና መስቀል በዓላት በሰላም እንዲከበር አስፈላጊውን ዝግጅት መደረጉ ተገልጿል

የሀረሪ ክልል ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ምክትል ሃላፊ ምክትል ኮሚሽነር ነስሪ ዘከሪያ ለክልሉ ብዙሃን መገናኛ ኤጀንሲ በሰጡት መግለጫ በክልሉ የመስቀል ደመራ በአል በሰላም እንዲከበር ለማስቻል በቂ ቅድመ-ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል። የበአሉን ፍፁም ሰላማዊነትን ለማረጋገጥ የተቀናጀ ስራ እየተካሄደ ስለመሆኑ ያመላከቱት ምክትል ኮሚሽነር ነስሪ የመስቀል ደመራ በሚከበርበትና በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ቋሚ፣ ተንቀሳቃሽና ስውር የፀጥታ አካላት መመደቡንም ጨምረው ገልፀዋል።

ለሰላም, ዜና

የመስተዳድር ምክር ቤቱ የኮሪደር ልማቱን ዘላቂነት የሚያረጋግጥ ደንብ አፀደቀ

የመስተዳድር ምክር ቤቱ የኮሪደር ልማቱን ዘላቂነት የሚያረጋግጥ ደንብ አፀደቀ ሀረር ነሀሴ 22/2016(ሀክመኮ):- የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት የኮሪደር ልማቱን ዘላቂነት የሚያረጋግጥ ደንብ አፀደቀ። የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ መስተዳድር ምክር ቤቱ (ካቢኔው) የደንብ ማስከበር ጽህፈት ቤትን እንደገና ለማቋቋም እና አደረጃጀቱን፣ ሥልጣንና ተግባራቱን ለማሻሻል በተዘጋጀ

Selam, ለሰላም, ዜና

በሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ሐኪም ወረዳ፣ አሚር ኑር ወረዳ ፣አባድር ወረዳ ፣ ድሬ ጠያራ ወረዳ ፣ ሸንኮር ወረዳ እና ኤረር ወረዳ የአብሮነት ቀን ተከብሯል

በሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ሐኪም ወረዳ፣ አሚር ኑር ወረዳ ፣አባድር ወረዳ ፣ ድሬ ጠያራ ወረዳ ፣ ሸንኮር ወረዳ እና ኤረር ወረዳ የአብሮነት ቀን ተከብሯል በሐኪም ወረዳ፣ አሚር ኑር ወረዳ ፣አባድር ወረዳ ፣ ድሬ ጠያራ ወረዳ ፣ ሸንኮር ወረዳ እና ኤረር ወረዳ በህዝቦች መካከል አብሮነትን በማጠናከር ሐገረ መንግሰት ግንባታን ለማስቀጠል እዲያስችል ከላይ በተጠቀሱትአምስት

Selam, ለሰላም, ዜና

በኮሪደር ልማት ስራው የተመዘገበው ውጤት በተሻለ ፍጥነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ርብርብ ይደረጋል- አቶ ኦርዲን በድሪ

ሀረር ነሀሴ 20/2016(ሀክመኮ):- በሀረሪ ክልል በኮሪደር ልማት ስራ የተመዘገቡ ውጤቶች በተሻለ ፍጥነት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ርብርብ እንደሚደረግ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ። የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ የሀረር ከተማን ስትራቴጂክ የልማት እቅድ ለመምራት ከተቋቋመው ግብረሃይል ጋር በከተማው እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች ላይ መክረዋል። በመድረኩም እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችን በተመለከተ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት

Selam, ለሰላም, በጎ ፈቃድ, ዜና

በሀረሪ ክልል በክረምት በጎ ፈቃድ መርሀ ግብር የታደሱና የተገነቡ 4 የአቅመ ደካማ ወገኖች መኖሪያ ቤቶች ተመርቀው ለተጠቃሚዎች ታላልፎ ተሰጠ

በሀረሪ ክልል በክረምት በጎ ፈቃድ መርሀ ግብር የታደሱና የተገነቡ 4 የአቅመ ደካማ ወገኖች መኖሪያ ቤቶች ተመርቀው ለተጠቃሚዎች ታላልፎ ተሰጠ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ በክረምት በጎ ፍቃድ ስራ በ3 ወረዳዎች የአቅመ ደካማ ወገኖች የታደሱና የተገነቡ 4 የመኖሪያ ቤቶችን በማስመርቅ የሐረር ክልል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ኦርዲን በድሪ እና ምክትል ፕሬዝዳንት ወይዘሮ ሮዛ ኡመር በተገኙበት ለተጠቃሚዎች ርክክብ አደርጉዋል።

ለሰላም, ዜና

ከተማውን ለነዋሪው ብሎም ለጎብኚዎች የተመቸ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው:- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ

ሀረር ሀምሌ 11/2016(ሀክመኮ):- የሀረር ከተማን ለነዋሪው ብሎም ለጎብኚዎች የተመቸ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ። የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ከከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ ጋር በመሆን የክረምት በጎ ፈቃድ ስራን አስጀምረዋል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በክልሉ ለ 5 መቶ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ፤ ለከተማ ውበት

Selam, ለሰላም, መግለጫዎች, ዜና, የሰላም እና ደህንነት

“የጠንካራ ፓርቲ ግንባታና በህዝብ ንቅናቄ ሁለንተናዊ ብልጽግና የማረጋገጥ ጉዟችን ” በሚል መሪ ሀሳብ በልሳነ ብልጽግና መጽሔት ዕትም ዙሪያ የጋራ ውይይት መድረክ ተካሄደ።

በዛሬው እለት የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ አና የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ የማሰረታዊ ደርጅት አመራሮችና ሰራተኞች “የጠንካራ ፓርቲ ግንባታና በህዝብ ንቅናቄ ሁለንተናዊ ብልጽግና የማረጋገጥ ጉዟችን “በሚል መሪ ሀሳብ በልሳነ ብልጽግና መጽሔት ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል። የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ቶፊቅ መሀመድ የመወያያ ጽሁፍ አቅርበው በዝርዝር ተወያይተዋል። በመድረኩ በዋናነትም የተቋማትን አቅም በማሳደግ የማህበረሰብ ተሳትፎና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት

Selam, ለሰላም, ዜና

በሀረሪ ፖሊስ ኮሚሽን የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊሳዊ አገልግሎት አባላት በሀረር ከተማ አራተኛ የገብርኤል በአል የሚከበርበትን ስፍራን አፅድተዋል።

በሀረሪ ፖሊስ ኮሚሽን የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊሳዊ አገልግሎት አባላት በሀረር ከተማ አራተኛ የገብርኤል በአል የሚከበርበትን ስፍራን አፅድተዋል። በሀረሪ ፖሊስ ኮሚሽን የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊሳዊ አገልግሎት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ግሩም ውብሸት የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ከማህበረሰብ አቀፍ ፖሊሳዊ አገልግሎት አባላት ጋር በመተባበር በሀረር ከተማ አራተኛ የሚገኘው የቁልቢ ገብርኤል አመታዊ የንግስ በአል የሚከበርበትን ስፍራ ማፅዳታቸውን ገልፀዋል። በተመሳሳይም የሰላም አደረጃጀቶቹ በሀረር

ለሰላም, ዜና, የሰላም እና ደህንነት

የገብርኤል አመታዊ የንግስ በአል በሰላም መጠናቀቁ ተገለፀ

የሀረሪ ክልል ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሀላፊ አቶ ቶፊቅ መሀመድ እንደገለፁት በቁልቢ ገብርኤል ከተከበረው አመታዊ የንግስ በአል በተጨማሪ በሀረር ከተማ አራተኛ ገብርኤል የተከበረው በአልም ፍፁም ሰላም በሰፈነበት መልኩ ተከብሮ በሰላም መጠናቀቁን ጠቁመዋል። በአሉ በሰላም መጠናቀቁ ሀረር የሰላም፣ የፍቅርና የመቻቻል ከተማ መሆኗና ህዝቦቿም ሰላም ወዳድ መሆናቸውን አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል። በአሉ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ አስተዋፅኦ ላደረጉት

Scroll to Top