በኮሪደር ልማት ስራው የተመዘገበው ውጤት በተሻለ ፍጥነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ርብርብ ይደረጋል- አቶ ኦርዲን በድሪ
ሀረር ነሀሴ 20/2016(ሀክመኮ):- በሀረሪ ክልል በኮሪደር ልማት ስራ የተመዘገቡ ውጤቶች በተሻለ ፍጥነት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ርብርብ እንደሚደረግ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ። የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ የሀረር ከተማን ስትራቴጂክ የልማት እቅድ ለመምራት ከተቋቋመው ግብረሃይል ጋር በከተማው እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች ላይ መክረዋል። በመድረኩም እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችን በተመለከተ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት […]